tg-me.com/nibab_lehiwot/158
Last Update:
ጥበቃ.......
"እንዴት የሚያምር ቀን ነው"። በሚል ሀይለቃል ነበር ቀኔን የጀመርኩት። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር በጠዋት የነቃሁት። ምክኒያቱም ለ 5 አመታት ሳልሰለች የጠበቅኩት ፍቅረኛዬ ይመጣል ። ለ አመታት ያሳለፍኳቸውን የጥበቃ ጊዚያቆች ሳስብ አንዳንዴ በፅናቴ እገረማለሁ። ከአሁን አሁን ይደውላል ጥበቃ፣ ከዛሬ ነገ ታገቢኛለሽ ብሎ ይጠይቀኛል ጥበቃ፣ ድንገት መጥቶ ሰርፕራይዝ ያደርገኛል ጥበቃ፣ ተኝቼ በህልሜ እስካየው ጥበቃ፣.................ብቻ ብዙ ብዙ ጥበቃ ለወትሮው እንደዚህ ትዕግስተኛ አልነበርኩም የያዘ ይዞኝ እንጅ........
ዛሬ ግን ይሄ ጥበቃየ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያበቃበት ቀን ነው። በቃ እፎይ የምልበት ቀን። ለዛም ነው በጠዋት ተነስቼ ቆንጆ ሆኜ የመጨረሻ ጥበቃየን ለመጠበቅ እየተዘጋጀሁ ያለሁት ። የሚወደውን ቆንጆ ሀምራዊ ቀሚስ አድርጌ፣ ፀጉሬን በግራ በኩል ከፍዬ ቆንጆ አድርጌ አስይዤዋለሁ። ጫማዬ ጥቁር ትንሽ ተለቅ ያለ ሄል ያለው ቆንጆ ጫማ ነው። ቦርሳዬ ዋው እሱ ድሮ የላከልኝ በጣም ምወደው ጥቁር ነጫጭ ፈርጥ ያለው ነው። በጊዜው ውድ የሚባለውን ሽቶ በላዬ ላይ አርከፍክፌ መስታወት ፊት ቆምኩ። መልኬ እንደዛሬ ቆንጆ ሆኖ ታይቶኝ አያውቅም። ብቻ ወጣሁ..............
ቦታው ጋ ደርሼ ሲመጣ ምን እንደምለው ፣ ከዛ በኋላ የምናደርጋቸውን ነገሮች፣ የሚኖረንን ሕይወት እያሰብኩ በደስታ አለም ውስጥ ራሴን አሰመጥኩት። ጠበቅኩ.....ጠበቅኩ...... ጥበቃው ሊሰለቸኝ ሲጀምር..... ለ አምስት አመት የጠበቅኩ ሴት አንድ ቀን መታገስማ አያቅተኝም ከዚህ በኋላኮ ላርፍ ነው ተመስገን እያልኩ ብቻየን እስቃለሁ። ብዙ ሰዓታት አለፉ ስልኩ አይሰራም........ሲመጣ መንገድ ላይ የሆነ ነገር ገጥሞት እንደሆነ ደመደምኩ። ነፍሴ ተጨነቀች...... ሳላገኘው ምን ሆኖብኝ ይሆን? ብቻ ውስጤ ፈራ....... ግን መጠበቅ አላቆምኩም ።ካለፉት አምስት አመታት ጥበቃ ይልቅ የዛሬው ጥበቃ እንደ ሺ አመት ረዘመብኝ። ............
ጥበቃው ቀጠለ። አንድ መልዕክት ስልኬ ጋር እስኪገባ ድረስ። እንዲህ ይል ነበር......
" የኔ ማር አትጠብቂኝ ለዘላለም አልመጣም!!!!"
የዛ ሁሉ አመት ጥበቃ በአንድ አረፍተነገር አከተመ!!!! "አልመጣም" መልዕክቱን ደጋግሜ አየሁት ውስጤ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ሲል ብቻ ተሰማኝ። አልጮህኩም፤ አላለቀስኩም። ምን እንደተሰማኝም አላውቅም ብቻ ግን ተሰበርኩ። ክንፏ እንደተመታ ወፍ ሙሽሽ አልኩ። ለካስ በጣም ሲታዘን እንባም ይደርቃል፣ ለመጮህም ቃላት ያልቃል።
ግን አንድ ነገር ልክ ነበርኩ። እንዳልኩት ዛሬ የመጨረሻ የጥበቃ ቀኔ ሆነ።ከዛሬ በኋላ አልጠብቅም!!!!
ከተቀመጥኩበት ተነስቼ በተሰበረ ልቤ ወደቤቴ መንገዴን ቀጠልኩ።
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/158